Wednesday, December 12, 2012

ዶሮና የሁለት ልጆች ፈተና


ምንጭ:-http://www.danielkibret.com

click here for pdf 
  ሁለት ተማሪዎች አንድ የቤት ሥራ ተሰጣቸው፡፡ የቤት ሥራው የተማሪዎችን ችሎታ ለመፈተን በከተማ ደረጃ የተዘጋጀ የዕውቀት መለኪያ ፈተና ነበር፡፡ ይህ ፈተና በሁለት ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ ተማሪዎች ተሰጥቷቸው ነበር፡፡ አንደኛው ተማሪ አባቱ የናጠጡ ነጋዴ ሲሆኑ እናቱም አሜሪካ ተወልደው አድገው በአንድ የውጭ ድርጅት ለመሥራት ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ናቸው፡፡ እርሱም የሚማረው ‹‹አበባ የቀጠፈና አማርኛ የተናገረ ይቀጣል›› የሚል ማስታወቂያ በተለጠፈበት አንድ የግል ትምህርት ቤት ነው፡፡ ሁለተኛው ተማሪ አባቱ የቀን ሥራ በመሥራት የሚተዳደሩ እናቱም ዶሮ የሚያረቡ ናቸው፡፡ ልጁም የሚማረው ከተቋቋመ ከሦስት ዓመቱ ጀምሮ መስኮቱ ተዘግቶ በማያውቅ አንድ የመንግሥት ትምህርት ቤት ውስጥ ነው፡፡

Monday, November 12, 2012

ከተራራው ጀርባ ያለው ሰው

ምንጭ:-http://www.danielkibret.com

እስኪ ታላቅ ነው በምንለው ቦታ ደርሰናል ብለን የምናስብ ሰዎች ለአፍታ ዘወር ብለን ተንጠላጥለንባቸው የተሻገርንባቸውን አያሌ ሰዎች ለማስታወስ እንሞክር፡፡ እዚህ ለመድረሳችን የምናውቀውንም የማናውቀውንም ድርሻ የተወጡ፣ እነርሱነታቸው እኛነታችን ውስጥ ያለ፡፡ አሁን የተቀመጥንበት ወንበር፣ የምንተኛበትም አልጋ፣ የምንኖርበትም ቤት፣ የምንቆጥረውም ብር፣ የወጣንበትም ከፍታ የእነርሱ ጭምር የሆነ፡፡ እነርሱ ባይኖሩ ኖሮ እዚህ ቦታ ለመድረስ ቀርቶ ወደዚህ አቅጣጫ እንኳን ለማየት የማይቻለን፡፡ እስኪ የሚቀጥለውን ታሪክ እየተከታተላችሁ እነዚህን አስቧቸው፡፡
መምህራን፣ የቤት ሠራተኞች፣ ሞግዚቶች፣ የሠፈር ሽማግሌዎች፣ አያት፣ አጎት፣ አክስት፣ የጥበቃ ሠራተኞች፣ ሾፌሮች፣ ጓደኞች፣ ሐኪሞች፣ ፖሊሶች፣ አንድ መሥሪያ ቤት ሄደን በጎ ያደረጉልን ሰዎች፣ ሳያስቡትም ሳናስበውም ዕድል የከፈቱልን ሰዎች፣ ሕይወታችንን የቀየረችውን አንዷን ብር የሰጡን ሰዎች፣ ከሞት ያተረፉን፣ ከመከራ የታደጉን ሰዎች፤ ያበረታቱን፣ ያጨበጨቡልን፣ የመረቁን፣ መንገድ ያሳዩን፣ በልብሳቸው አጊጠን፣ በምግባቸው ጠግበን እንድንጓዝ የረዱን፤ ከኛ በፊት ሕይወታቸውን ሰጥተው፣ ለኛ ሲሉ ተሠውተው ያለፉልን ጀግኖች፤ እነማን ነበሩ? እስኪ ይህንን ታሪክ እያነበባችሁ አስቧቸው፡፡

Friday, November 2, 2012

መንፈሳዊነት፦ ክፍል ፩

ምንጭ:-http://www.betedejene.org/


የሰው መንፈሳዊነት ከመንፈስ ቅዱስ ነው። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን፦ “እነሆ እኔ የአባቴን ተስፋ ለእናንተ እልካለሁ (በነቢዩ በኢዩኤል የተነገረው ትንቢት ይፈጸምላችኋል) እናንተ ግን ከአርያም ኃይልን እስክትለብሱ በኢየሩሳሌም ከተማ ተቀመጡ።” ያላቸው ለዚህ ነው። ኢዩ. ፪፥፳፰-፴፪ ፣ ሉቃ ፳፬፥፵፱። እነርሱም ተስፋውን አምነው ለአሥር ቀናት ጸንተው በመቆየታቸው ለአሥሩ መንፈሳውያት ማዕረጋት የሚበቁበትንና በአሥሩ የመላእክት ከተሞች እንዳሉ ቅዱሳን መላእክት የሚተጉበትን ጸጋ በእሳትና በነፋስ አምሳል አግኝተዋል። የሐ ፪፥፩-፬።

Thursday, November 1, 2012

Wednesday, October 31, 2012

118ኛው ፓትርያርክ መንገድ ላይ ናቸው

 ምንጭ :-http://www.danielkibret.com/2012/10/118.html#more

ዐቃቤ መንበር አቡነ ጳኩሚስ ድምጽ ሲሰጡ
የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን 118ኛውን ፓትርያርክ የመምረጡ ሂደት ወደ መጨረሻው ምዕራፍ ተሻግሯል፡፡  በቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግ መሠረት አዲስ ፓትርያርክ ለመምረጥ አራት ሂደቶችን ማለፍ ያስፈልጋል፡፡ የጥቆማና ማጣራት፣ የመጨረሻዎቹን አምስት ዕጩዎች የመወሰን፣ ለዕጣ የሚቀርቡትን ሦስት አባቶችን መምረጥና የመጨረሻውን አባት በዕጣ መምረጥ ናቸው፡፡
በዚሁ መሠረት ከተጠቆሙት ወደ አሥራ ሰባት አባቶች መካከል የማጣራቱና አምስቱን የመወሰኑ ሂደት እጅግ ረዥም ጊዜ የወሰደ መሆኑ ታውቋል፡፡ ይህ ሂደት ሁለት ከባባድ ችግሮች ተጋርጠውበት ነበር፡፡ የመጀመርያው ፈተና በቤተ ክርስቲያኒቱ ቀኖና ከተጻፈውና የግብጽ ቤተ ክርስቲያንም ሕግ ከሚደነግገው ውጭ ሀገረ ስብከት ያላቸው አባቶች ራሳቸውን ሳይቀር ለዕጩነት መምረጣቸው፣ ከዚህ በፊት አንዳንድ ችግሮች ተከስተውባቸው የነበሩ አባቶችም በዕጩዎች ዝርዝር ውስጥ መግባታቸው ነበር፡፡
ይህ ሁኔታ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ቀኖናና ሕግ ጋር የሚጋጭ በመሆኑ ራሳቸውን ከዕጩነት እንዲያገልሉ በአስመራጭ ኮሚቴውና በቤተ ክርስቲያኒቱ ታላላቅ አባቶችና ሽማግሌዎች የማግባባትና የማረም ሥራ ሲሠራ ነበር፡፡ ለሁለት ጊዜ ያህል ሱባኤ ታውጆ፣ ጳጳሳቱም ሁሉ ወደ አባ ብሶይ ገዳም ገብተው በጸሎትና በውይይት ችግሩን ለመፍታት ጥረት አድርገዋል፡፡ በዚህም ምክንያት የተወሰኑት አባቶች ‹እኔ በሺኖዳ መንበር መቀመጥ የለብኝም› እያሉ ራሳቸውን ከዕጩነት አግልለዋል፡፡ 
ከዚያ በኋላም ቢሆን የዕጩዎቹ ቁጥር በመብዛቱና በምእመናኑም ዘንድ በአንዳንድ ዕጩዎች ላይ ቅሬታ በመፈጠሩ የምርጫ ኮሚቴው ጊዜ ወስዶ ችግሮቹን ለመፍታት ሞክሯል፡፡ እጅግ የባሰው ሁለተኛውም ፈተና የተጀመረው በዚህ ጊዜ ነበር፡፡
አንዳንድ ዕጩዎች በቴሌቭዥን ፕሮግራም ሳይቀር ልክ እንደ ፖለቲካ ተመራጮች የምረጡኝ ዘመቻ ጀመሩ፡፡ ሕዝቡ ግራ ተጋባ፡፡ ዐቃቤ መንበሩ አባ ጳኩሚስ አንዳንድ ክርስቲያን የቴሌቭዥን ጣቢያዎችን እስከ ማስጠንቀቅ ደረሱ፡፡ በዚህ ጊዜ ምእመናኑና አባቶች በወሰዱት ቆራጥ አቋምና ግፊት አንዳንድ እጩዎች ከዕጩነት እንዲወጡ ተደረገ፡፡ በመጨረሻም አምስት አባቶች ቀሩ፡፡ በዚህ ሂደትም አምስት ጳጳሳትና ሰባት መነኮሳት ከዕጩነት ወጡ፡፡ በሂደቱ ከዕጩነት ከወጡት መካከል የሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ አቡነ ቢሾይ፣ የቀድሞው ፓትርያርክ ረዳት የነበሩት አቡነ ቡትሮስና የመንበረ ፓትርያርኩ ዋና ጸሐፊ አቡነ ዮሐንስ ይገኙበታል፡፡ 
በግንቦት ወር የተጀመረው 118ኛውን ፓትርያርክ የመምረጡ ሂደት ባለፈው ሰኞ ወደ መጨረሻው ደረጃ ተሸጋግሯል፡፡ ሰኞ ዕለት በካይሮ አባስያ በሚገኘው የቅዱስ ማርቆስ ካቴድራል ከአምስቱ አባቶች ሦስቱን በድምጽ የመለየት ሂደት ተከናውኗል፡፡
የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ሕግ እንደሚፈቅደው ብቃት ያላቸው የሚባሉት ድምጽ ሰጭዎች ቁጥራቸው 2411 ነው፡፡ እነዚህ ድምጽ ሰጭዎች በቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር ሥር ያሉ ካህናት፣ የገዳማት ተወካዮች፣ የምእመናን ተወካዮች፣ በግብጽ ፓርላማ ወንበር ያላቸው የኮፕት ማኅበረሰብ ተወካዮች፣ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ተወካዮችና ክርስቲያና ጋዜጠኞችን ያካተተ ነው፡፡

Tuesday, October 30, 2012

እውነታ - ማንጠር (Fact Checking)

ምንጭ :-http://www.adebabay.com/2012/10/fact-checking.htm

(ኤፍሬም እሸቴ/adebabay.com/ PDF)፦ አሜሪካ አዲስ ፕሬዚዳንት ለመምረጥ ደፋ ቀና እያለች ነው። ሁለቱ እጩዎች ማለትም ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ እና የማሳቹሴትስ ገዢ የነበሩት ሚት ራምኒ እረፍት የላቸውም። ከደጋፊዎቻቸው ያሰባሰቡት በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር በተለይም ወሳኝ በሚባሉ ግዛቶች ከፍ ላለ የማስታወቂያ ክፍያ በዋል ላይ ይገኛሉ። ከማስታወቂያውም ባሻገር ራሳቸው ተወዳዳሪዎቹም በመላው አገሪቱ በመዞር የምረጡኝ ዘመቻ በማካሔድ ላይ ናቸው።

እያንዳንዱ ወሳኝ ቲቪ እና ሬዲዮ ጣቢያ ዋነኛ የፖለቲካ ዓምድ ይኸው ምርጫ ነው። በአገሪቱ ታዋቂ የሆኑ “ቶክ ሾዎች” (ማለቴ ፖለቲካ ቀመስ ቶክ ሾዎች) በዚሁ ምርጫ ዙሪያ ሰፊ ትንተና ያቀርባሉ፤ ይከራከራሉ። ያለኹበትን አካባቢ ለመጥቀስ ሞከርኩ እንጂ እያንዳንዱ ከተማ እና አካባቢ ባሉት ኤፍ.ኤም ሬዲዮኖች የሚያቀርቡትን በሙሉ መስማት አልችልም። ለመገመት ግን ይቻላል።

የዚህ ሁሉ የቲቪና ሬዲዮ እንዲሁም የጋዜጣ ትንተና እና ውይይት መድረሻና መዳረሻ “እውነታን ማንጠር”፣ ሐሳብን እና አመለካከትን መሞረድ፣ ወይም ገለባን ከምርቱ እንደማንጠርጠር፣ በሰፌድ በወንፊት እንደማጣራት ዓይነት ነው። በዚህ ውይይት የሚንጠረጠረውና የሚጣራው እውነታው ከሐሰቱ፣ ጠቃሚው ከማይጠቅመው ነው። ይኸው የአንዱ መስመር ከሌላው የሚለይበት የሐሳብ ማንጠርጠሪያ ገበታ በሌላ አነጋገር “ነጻ ሚዲያ” ልንለው እንችላለን።

ከ“ነጻ ሚዲያው” መካከል ዜናውንና ሐተታውን ከማቅረብ ባሻገር በሁሉም መስክ የሚባለው፣ የሚነገረው፣ የሚጻፈው፣ የሚተነተነው ጉዳይ ትክክል መሆን አለመሆኑን ቀድመው በማረጋገጥና ለዚህም ከፍተኛ ግምት በመስጠታቸው የሚታወቁ ጥቂት የዓለም ሚዲያዎች አሉ። ከነዚህም ውስጥ የጀርመኑን ሳምንታዊ መጽሔት “ዴር ሽፒግል”ን (Der Spiegel) የሚያክል የለም። (“ኒውዮርክ ታይምስ”ን የመሳሰሉት ጭምር።)

Tuesday, January 31, 2012

በአንድ የዘመዴ ቤት አንድ ዘመዴ ቤት ሄጄ ነው፡፡ እናቱ «እስኪ ያንን ነገር ለዳንኤል አሳየው» አለቺው ልጇን፡፡ ልጇ የአራተኛ ክፍል ተማሪ ነው፡፡ ደብተሩን ይዞት መጣ፡፡ ትናንት ሠርቶ ዛሬ ባሳረመው የአማርኛ የቤት ሥራ ሁለት ኤክስ አግኝቷል፡፡ ልጁ ግን ለምን ኤክስ ሊሆን እንደቻለ ሊገባው አልቻለም፡፡ እናቱን ደጋግሞ ጠየቃት፡፡ እርሷም ግልጽ አልሆነላትም፡፡ የተሰጠው ጥያቄ አዛምድ ነው፡፡ እዚያ መካከል «እንደ ወትሮው» የሚል ሐረግ በ «ሀ» ሥር ይገኛል፡፡ በ «ለ» ሥር ደግሞ «እንደ ሁልጊዜው» የሚል ምርጫ አለ፡፡ ልጁ የመጀመርያውን ኤክስ ያገኘው እነዚህን በማዛመዱ ነበር፡፡ ከዚያው በታች በ«ሀ» ሥር ላለው «መሞከር» ለሚለው ቃል «መጣር» የሚል ተዛማጅ በ«ለ» ሥር ተቀምጧል፡፡ የሚል ሌላ አዛምድ አለ፡፡ ልጁ ከተሰጡት መልሶች ተቀራራቢ የሆነውን መልሷል፡፡ መምህሩ ግን አላረመለትም፡፡ እኔንም ጥያቄ ፈጠረብኝ፡፡ ይበልጥ ያስገረመኝ ደግሞ ትክክለኛው መልስ ምን እንደሆነ አለመጻፉ ነው፡፡ ልጁን «መልሱ ምንድን ነው አላችሁ?» ብዬ ጠየቅኩት፡፡ «ኤክስ አደረገኝ እንጂ መልሱን አልጻፈልኝም» አለኝ፡፡ መምህሩ ደብተራቸውን ወስዶ ኖሯል ያረመው፡፡ «እስኪ መጽሐፉን አምጣ» አልኩና ጥያቄዎቹን መመልከት ጀመርኩ፡፡ አሁን ነገሩ ግልጽ ሆነልኝ፡፡ ልጁ «መ»ን እና «ሠ»ን ሲገለብጥ አቀያይሯቸዋል፡፡ መምህሩም የአዛምዱን መልሶች ያረመው ፊደላቱን እያየ እንጂ መልሱን እያየ አይደለም፡፡ ይህ ግን በልጁ ላይ ሁለት ነገር ፈጠረበት፡፡ አንደኛ ለምን ኤክስ እንዳገኘ ሊገባው አልቻለም? ሁለተኛ ደግሞ የእነዚህን ሐረጋት ትርጉም ሊያውቅ አልቻለም፡፡ ምክንያቱም እርሱ ትርጉም ነው ብሎ የሰጠው መልስ ስሕተት ነው ተብሏል፡፡ ትክክለኛው ደግሞ አልተነገረውም፡፡