የመስቀል
በዓል የሚከበረው መስከረም ፲፯ ነው። ይህም በዓል በክርስቲያኑ ዓለም ሁሉ ይከበራል። የቤተ ክርስቲያን ታሪክ
እንደሚነግረን ጌታ በመስቀል ሞቶ ከተነሳ በኃላ ሕሙማን መስቀሉን እየዳሰሱ በመስቀሉ እየታሹ ይፈወሱ ነበር።በዚህ
በዙዎች የክርስትና እምነት ተከታዮች ሆኑ በክርስቶስ አመኑ። ይህንን የተመለከቱ አይሁድ መስቀሉን በአንድ ቆሻሻ
መጣያ ቦታ ጣሉት የአካባቢው ኗሪ በዚያ ቆሻሻን እንዲጥል አደረጉት ስፍራውም እንደ ተራራ ጉብታ ሆነ፤ መስቀሉ
በዚህ ስፍራ ለሶስት መቶ ዓመታት ቆይቷል። በ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የንጉስ ቆስጠጢኖስ እናት ንግስት እሌኒ ይህን
ታሪክ ትሰማ ነበርና ጉዞዋን ወደእየሩሳሌም ቀጠለች። በስፍራው ያለውን ጉብታ ቦታ ብታስቆፍርና በአካባቢው
የሚገኙትን ብትጠይቅ ልታገኘው አልቻለችም ይሁንና መስቀሉ እንዲወጣ የእግዚአብሔር ፍቃድ ስለነበረ አንድ አረጋዊ
ስሙ ኪርያኮስ የሚባል የእሌኒን መቸገር አይቶ እንደሚከተለው ይመክራታል። " አንቺም በከንቱ አትድከሚ ስውንም
አታድክሚ እንጨት አሰብስበሽ እጣን አፍሽበት በእሳትም አያይዢው የእጣኑ ጢስ ወደላይ ወጥቶ ወደታች ሲመለስ
አቅጣጫውን አይተሽ አስቆፍሪው በዚህ ምልክት ታገኚዋለሽ አላት እርሷም ያላትን ሁሉ አደረገች። በዚህም ታላቅ
ምልክት የተደበቀውን መስቀል አውጥታዋለች።
በመስከረም
፲፮ ባላገሩ በቀበሌው የከተማው ህዝብ በተዘጋጀለት ቦታ ከየቤቱ ችቦውን እንጨቱን እያመጣ ይደምራል። ካህናቱም
በደመራው ፊት ለፊት ጸሎት አድርሰው " መስቀል አብርሃ በክዋክብት አሰርገወ ሰማየ እምኩሉሰ ፀሐየ አርአየ" እያሉ
ደመራውን ይዞራሉ ቀጥሎም ህዝቡ "እዮሀ አበባዬ መስከረም ጠባዬ" እያሉ በደመራው ዙሪያ ይጨፍራሉ። ማታ ሕዝቡ
ችቦውን እያበራ ደስታውን ሲገልጥ ያመሻል በ፲፯ ጧት ደመራው ይለኮሳል አመድ እስኪሆን ድረስ ይቃጠላል ደመራው
የተጸለየበትና የተባረከ ስለሆነ ሕዝቡ አመዱንና ትርኳሻውን እየተሻማ ወደ ቤቱ ይዞ ይሔዳል። ለሰውም ሆነ ለከብት
መድኃኒት ሆኖ ያገልግላል።
ምንጭ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ በብፅ አብነ ጎርጎርዮስ የሸዋ ሊቀ ጳጳስየመስቀሉ ቃል
ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።የጥበበኞችን ጥበብ አጠፋለሁ የአስተዋዮችንም
ማስተዋል እጥላለሁ ተብሎ ተጽፎአልና።ጥበበኛ የት አለ? ጻፊስ የት አለ? የዚች ዓለም መርማሪስ የት አለ?
እግዚአብሔር የዚችን ዓለም ጥበብ ሞኝነት እንዲሆን አላደረገምን?በእግዚአብሔር ጥበብ ምክንያት ዓለም እግዚአብሔርን
በጥበብዋ ስላላወቀች፥ በስብከት ሞኝነት የሚያምኑትን ሊያድን የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ሆኖአልና።መቼም አይሁድ
ምልክትን ይለምናሉ የግሪክ ሰዎችም ጥበብን ይሻሉ፥እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ይህም ለአይሁድ
ማሰናከያ ለአሕዛብም ሞኝነት ነው፥ (፩ኛ ቆሮ 1፡18)